ኢትዮጵያ ቻይና ኢንዶኔዢያ እና ካይሜን በቦይንግ 737 ማክስ 8 የሚደረጉ በረራዎችን አገዱ


የኢትዮጵያ አውሮፕላን
ሃገራቱ በረራዎቹን ያገዱት ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 737 አውሮፕላን ትላንት መከስከሱን ተከትሎ ነው፡፡
ቦይንግ 737 ማክስ 8 ከተባለው አውሮፕላን ጋር በተያያዘ አደጋ ሲከሰት ባለፉት ስድስት ወራት ይህ ሁለተኛው ነው።
የንግድ በረራ የሚያካሂዱ የኢትዮጵያ የቻይና ኢንዶኔዢያ እና የካይሜን አየር መንገዶች አውሮፕላኑን መጠቀም አይችሉም ተብሏል።
ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 737 አውሮፕላኑ ከቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የተነሳው እሁድ ጠዋት 238 ሲሆን 6 ደቂቃ በኋላ ከአብራሪዎቹ ጋር ይደረግ የነበረው ግንኙነት ተቋርጦ ከደቂቃዎች በኋላ ቢሾፍቱ አካባቢ መከስከሱን ነው የአየር መንገዱ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም የተናገሩት ።
ቻይና  አውሮፕላን

በአደጋውም ስምንት የአየር መንገዱ ሰራተኞችን ጨምሮ 157 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል

የአውሮፕላኑ አምራች ኩባንያ ቦይንግ በበኩሉ በተፈጠረው አደጋ እጅግ ማዘኑን በመግለጽ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥና የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት በሚደረገው ስራ ላይ እርዳታ የሚሰጥ ቡድን እንደሚልክ አስታውቋል።
የምርመራ ሂደቱም የሚመለከታቸው የኢትዮጵያ መስሪያ ቤቶች ከቦይንግ ባለሙያዎችና ከአሜሪካ የትራንስፖርት ደህንነት መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር የሚካሄድ ነውም ተብሏል።
ባለፈው ጥቅምት ''የላየን'' አየር መንገድ ንብረት የሆነ ተመሳሳይ አውሮፕላን ተከስክሶ 189 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።
ካይሜን  አውሮፕላን
የቻይናው ሲቪል ኤቪየሽን ባለስልጣን በአጭር ጊዜ ውስጥ አንድ የአውሮፕላን ሞዴል አደጋ ሲደርስበት በቸልታ ማለፍ እንደሚከብደው ገልጿል።
በትናንትናው ዕለት በቦይንግ 737 በረራ ቁጥር ET302 157 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈው አሰቃቂ አደጋ የ33 ሃገራት ዜጎች እንደነበሩበት ይታወሳል፡፡

የቻይና አየር መንገዶች የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላንን መጠቀም የሚችሉት የኤቪዬሽን መስሪያ ቤቱ ወደፊት በሚሰጠው መግለጫ መሰረት እንደሆነ አስታውቋል።
           የኢትዮጵያ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ስባሪ
በትናንትናው ዕለት በቦይንግ 737 በረራ ቁጥር ET302 157 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈው አሰቃቂ አደጋ ከሟቾቹ መካከል 8 ቻይናዊያን መሆናቸው ታውቋል።



Post a Comment

0 Comments