ኦማር አልበሽር ከ30 ዓመት በኋላ ስልጣን ማስረከባቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡


በመጨረሻም ኦማር አልበሽር ከ30 ዓመት በኋላ ስልጣን ማስረከባቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
·        ሱዳን የዳቦ እና የነዳጅ ዋጋ መጨመር ተከትሎ የተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ እያደር ኦማር አልበሽር ስልጣን ይልቀቁ ወደሚል ከረር ያለ ተቃውሞ ተቀይሮ ቆይቷል፤
·        ተቃውሞው ከ8 ቀናት በኋላ 5 ወር ይሞላዋል፡፡ በነዚህ ወራትም አብዛኞቹ የሃገሪቱ ዋና ዋና መንገዶች በተቃዋሚዎች  ተጨናንቀው ቆይተዋል
·        የሃገሪቱ ፖሊስ ተቃዋሚዎችን ለመበተን አስለቀሽ ጭስ ሲጠቀም ቆይቷል፡፡
·        እየበረታ የሄደው ተቃውሞ መልኩን በመቀየሩ የሃገሪቱ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አውጇል፤ ቢሆንም ግን ተቃውሞውን ሊገታ አልቻለም፡፡
·        ጋዜጠኞች በማይታወቅ ስፍራ ታስረዋል፤ ሁለት በዓረቢኛ ቋንቋ የሚሰሩ የዜና ጣቢያዎችም ፈቃዳቸው ተሰርዞ በሃገሪቱ እንዳይሰሩ ተከልክለዋል፡፡
·        የሱዳን መንግስት በዚሁ ምክንያት 31 ሰዎች መገደላቸውን ሲገልፅ human rights watch ደግሞ 51 ሰዎች ተገድለዋል ብሏል፡፡
·        የኋላ ኋላ የ75 ዓመቱ ፕሬዝደንት ኦማር አልበሽር ከህዝቡ ጋር መነጋገር እንደሚፈልጉ ተናግረው ነበር ህዝቡ ግን አልተቀበላቸውም፡፡
·        በመጨረሻም ኦማር አልበሽር ከ30 ዓመት በኋላ ዛሬ ስልጣን አስረክበዋል፡፡
·        የፈረንጆቹ 2019 ዓመት ከገባ ወዲህ የቀድሞው የአልጀሪያው ፕሬዝደንት አብዱላዚዝ ቡቶፍሊካን ተከትለው በህዝባዊ ተቃውሞ ስልጣን ያስረከቡ በአፍሪካ ሁለተኛው  መሪ ናቸው፡፡

Post a Comment

0 Comments